Announcement የልደታ ማንፋክቸሪንግ ኮሌጅ የቴክኖሎጂ ልማትና ኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን ዳሬክቶሬት

የልደታ ማንፋክቸሪንግ ኮሌጅ የቴክኖሎጂ ልማትና ኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን ዳሬክቶሬት

14th October, 2025

የልደታ ማንፋክቸሪንግ ኮሌጅ የቴክኖሎጂ ልማትና ኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን ዳሬክቶሬት ከልደታ ክፍለ ከተማ ስራና ክህሎት ፅ/ቤት እና ከወረዳ ባለሙያዎች ጋር በመሆን የአዲስ ኢንተርፕራይዝ እርክክብ እና  ድጋፉን ውጤታማነትን ለማረጋገጥ በቀጣይ በጋራ ለመስራት የሚያስችላቸውን ውይይት አደረጉ።

ወ/ሮ የሺወርቅ እንየው እደተናገሩት ዛሬ በሰነድ የተረከብናቸውን ኢንተርፕራይዞችን በቀጣይ በጋራ የአካል እርክክብ የሚደረግ መሆኑን አስገንዝበው በቀጣይም  የድጋፍ ስራችንን ውጤታማ ለማድረግ  በጋራ  አጠናክረን መቀጠል አለብን ብለዋል።

የልደታ ክፍለከተማ ስራና ክህሎት ፅ/ቤት ተወካይ ወ/ሮ ዝናሽ ዘውዴ በበኩላቸው እንተርፕራይዞች የተለዩት ለኮሌጁ ቅርበት ያለውን ወረዳዎች ማለትም ወረዳ 1, 2, 3, 5. እና 7 ሲሆኑ ኮሌጁ የሚሰጠውንም ድጋፍ ከኮሌጁ ጋር በጋራ ሆነው የሚከታተሉ የየወረዳ ተወካይ ባለሙያዎች በመመደብ በጋራ እንድንወያይ የደረጉ በቀጣይ ለሚኖረው የመረጃ ልውውጥ ወጥ የሆነና ተናባቢ ስራ መስራት ያስችለናል ብለዋል።

.

Copyright © All rights reserved.

Created with